(መሠረት ሚድያ)- በርካታ የግል ባንኮች ሰራተኞቻቸውን በአስገዳጅነት ህብረተሰቡን የባንክ አካውንት እንዲያስከፍቱ ተልዕኮ እየተሰጡ መሆናቸውን የሚገልፅ አንድ አስተያየት በትናንትናው እለት ማስነበባችን ይታወሳል።
በዚህ አስተያየት ላይ "የግል ባንኮች ሰራተኞች ላይ ከዲስትሪክት ጀምሮ በየቀኑ እየተደወለ አንዳንዴም ወደ ቅርንጫፎች እየመጡ ሰራተኞቹ ማድረግ የማይችሉትን ትዕዛዝ በመሥጠት ያን ካላደረጉ ደግሞ ከደሞዛቸው ጀምሮ ብዙ ቅጣቶች እንደሚጠብቃቸው እያስፈራሩ ብቻም ሳይሆን እያደረጉትም ይገኛሉ" የሚል አስተያየት በፀሀፊው አቶ ፍቃዱ ኤርሱሞ ተንፀባርቋል።
ዛሬ የምናስነብባችሁ ደግሞ ባንኮች ውስጥ በሹፌርነት ተቀጥረው የሚሰሩ ሰራተኞች እያንዳንዳቸው በድምሩ 4 ሚልየን ብር የሚሆን የባንክ አካውንት እንዲያስከፍቱ ስለታዘዙ ሹፌሮች ነው።
ጉዳዩ እንዲህ ነው፣
አዋሽ ባንክ እንደሌሎቹ ባንኮች ሁሉ ገንዘብ ለማሰባሰብ ሰራተኞቹን በከተማው ከማሰማራቱ ውጪ ሹፌሮቹም እያንዳንዳቸው 4 ሚልየን ብር deposit አስደርጉ መባላቸውን ሰማን።
"ሹፌሩ መኪናውን በአግባቡ መንዳት ትቶ ስለ ገንዘብ ማሰባሰብ ሲያስብ እና ሲጨነቅ ነው የሚውለው" ያሉን አንድ የተቋሙ ሰራተኛ ሁሉም ሹፌሮች እስከ ሰኔ አጋማሽ ግባቸውን እንዲመቱ (4 ሚልየን ብር ከህዝቡ deposit እንዲያስደርጉ) መታዘዛቸውን ተናግረዋል።
መሠረት ሚድያ የተመለከው አንድ የባንኩ ሰራተኞች የመልዕክት መለዋወጫ ግሩፕ ላይ የተፃፈ መረጃ ይህንኑ የሚያረጋግጥ ሲሆን "እያንዳንዱ የባንኩ አሽከርካሪ መኪና መንዳት ብቻ ሳይሆን ሀብት በማሰባሰብ ዘመዶቹን እና ጓደኞቹን ቡክ በማስከፈት አዳዲስ ደንበኞችን ማምጣት አለበት" ይላል።
መልዕክቱ አክሎም "አንድ አሽከርካሪ 4 ሚልዮን ብር ቢያመጣ የታለመውን እቅድ በቀላሉ ከግብ እናደርሳለን፣ ከዛሬ ጀምሮ እስከ ሰኔ አጋማሽ ድረስ በተሰጣችሁ እቅድ መሰረት እያንዳንዳችሁ ለጉዳዩ ትኩረት በመስጠት እንድትተባበሩ" ይላል።
ደህና ኑሮ ይኖራሉ የሚባሉትን ጨምሮ በርካታ የህብረተሰብ ክፍል ኑሮው ከእጅ ወደ አፍ በሆነበት በዚህ ወቅት አንድ ሹፌር በምን መልኩ 4 ሚልዮን ብር የሚያወጣ ቡክ ማስከፈት እንደሚችል ለበርካቶች ጭንቀትን ብቻ ሳይሆን አስደማሚ ሆኗል።
በዚህ ዙርያ ከባንኩ መረጃ ከደረሰን እናቀርባለን።
መረጃን ከመሠረት!
አረ ስቃይ ነው ወንድሜ እኔ ዳሽን ባንክ ውስጥ ነው የምሰራው ፡ይኸው 2 ዓመት ሞላኝ አዲስ ደንበኛ ማምጣት (Account Opening ) የግድ በሳምንት ውስጥ የሚሰጥህ ቁጥር አለ እሱን መሙላት አለበት አለበለዚያ ከደሞዝ ቅጣት ጀምሮ በፐርሰንት እስከ የመጨረሻ የፅሁፍ ማስጠንቀያ ድረስ በዚህ ጉዳይ ብቻ ይደርስሀል ፡ ከዛ እንደምንም እሱን ተወጣው ስትል ደሞ ያስከፈትካቸው አካውንቶች ዲፕዚት በኳርተር ተብለህ ይሄን ያህል ሚሊዮን ብር ማምጣት አለብህ ፡ አለበለዚያ ያው ከዲስትሪክት ጀምሮ የብራንቹ ማናጀር ድረስ አንተ ላይ ነው ዱላው ፡ በዚህ አጋጣሚ አይነ ውሀህ ካልተመቸው ብራንች ማናጀሩ አዲስ ደንበኛ ስላላመጣህ በበቂ ሁኔታ እና Deposit በቂ ስላላመጣህ ተብዬ ደብዳቤ ተፅፎብኝ እኔው እራሴ ከ 5ወር በፊት ይኸው አሁን ባየው ባየው የሚዘለቅ አለመሆኑ ሲገባኝ መልቀቂያ አስገብቻለሁ ፡ በፈቃዴ ስራውን ልለቅ በዚህ ምክንያት፡፡ ቀጣይ ምን እንደምሰራ እራሱ ግራ ግብት ብሎኛል ፡ በቤት ኪራይ ነው የምኖረው፡ ዕድሜዬ 29 ነው ፡ በቢዝነስ ማኔጅመንት ዲግሪ አለኝ ፡ እንዲሁም Master Of Business Adminstration (MBA) ማስተርስ አለኝ ፡ ከንቱ ልፍት ሆነብኝ ይኼ ሁሉ ዓመት አፈር ድሜ በልቼ ፡ ስራ እየሰራው እራሴን አስተምሬ ፡ ይኸው ሆነ የድካሜ ፡ ውጤት ፡ በጣም ያሳዝናል ። እረጅም ጊዜ ሌሊት ሁሉ ጭምር አሁን ከየት ነው አዲስ ደንበኛ የማገኘው፡ዲፖሲትስ ማን ይኼን ሁሉ ሚሊዮን ብር አለኝ ብሎ ባንኩ ላዮ Deposit የሚያደርገው እያልኩ ከልክ በላይ በመጨነቄ የተነሳ Mental Stress ታምሜ ህክምና እየተከታተልኩ ነው ፡የመንግስት ሆስፒታል፡ ፈጣሪ በሚያውቀው፡ በዚህ ደረጃ ነው ችግሩ ያለው ለማለት ነው፡መሰረት ከልብ እናመሰግናለን የልባችንን፡ሰው እንዲያውቅልን ስላደረስክልንThank You So Much ዕድሜና ጤና ይስጥህ !!!
መሠረት ከልብ እናመሠግናለን እኔ የአዋሽ ባንክ ሠራተኛ ነኝ በግል በገኝህና የሠራተኝነት መረጃዎቼን አሣይቼህ ቃሌን በ audio ጭምር ብሠጥ ደስ ይለኛል ። እዚ ቤተሠብ ያለን ሠዎች ተምረን የልመና ስራ ከምንሠራ ብለን እየለቀቅን ነው አዋሽ ባንክ ሠራተኞቹን ልመና መሣራት ጀምሮዋል። ጥያቄ ስንጠይቅ ስራ አጥ ሞልቶዋል ካልፈለጋቹ ልቀቁ ነው ሚሉን ከባለ ሞያነት ወደ ባርያነት ቀይረውናል።